አንድ ሺህ 438ኛው የኢድ አልፈጥር በአል በመላው አለም ተከበረ

ኢሳት (ሰኔ 19 ፥ 2009)

በአዲ አበባ ታላቁ አንዋር መስጊድና በሌሎች የኢትዮጵያ አካባቢዎች የተከበረው የኢድ አልፈጥር በአል ኢትዮጵያውያን በከፍተኛ ቁጥር በተገኙበት ዩ ኤስ አሜሪካ በተለይም በዋሽንግተን ዲሲ በደማቅ ስነ-ስርዓት መከበሩን ዜናው ያስረዳል።

የፈርስት ሂጂራ ፋውንዴሽን ኢማም ሼህ ካሊድ ኡመር እና የፋውንዴሽኑ ፕሬዝዳንት ሃጂነጂብ መሃመድ በተገኙበት በዋሽንግተን ዲሲ አቅራቢያ ቨርጂኒያ ግዛት በተከበረው የኢድ አልፈጥር በአል ሙስሊሙ ማህበረሰብ በብዛት መገኘቱም ታውቋል።

በከፍተኛ ሃይማኖታዊ ስርአት በአሉ መከበሩና ሃይማኖታዊ እንዲሁም ሃገራዊ መልዕክቶች መተላለፋቸውም ታውቋል።