አልሸባብ ፕሬዚዳንት ኦባማንና ውጭ ጉዳይ ሚኒሰትሩዋን ለመግደል የሚያስችል መረጃ ለሚሰጡ ሁሉ እንደሚከፍል አስታወቀ

ሰኔ ፪ (ሁለት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-አልሸባብ ፕሬዚዳንት ኦባማንና ውጭ ጉዳይ ሚኒሰትሩዋን ለመግደል የሚያስችል መረጃ ለሚሰጡ ሁሉ ገንዘብ እንደሚከፍል አስታወቀ የሶማሊያ ታጣቂ ሀይል ይህን መልስ የሰጠው የባራክ ኦባማ አስተዳዳር የአልሸባብ መሪዎች ያሉበትን ለጠቆመ ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚሰጥ ማስታወቁን ተከትሎ ነው።

የአልሸባብ የቆዩ መሪ የሆኑት ሼክ ሾንጎሌ እንደተናገሩት ፕሬዚዳንት ኦባን ለመግደል የሚያስችል በቂ መረጃ ለሚያመጣ ሰው 10 ግመሎችን ይሸልማሉ፤ በአንጻሩ ሂላር ክሊንተንን በተመለከተ ለሚመጣ መረጃ ደግሞ 10 ሴትና 10 አውራዶሮውችን እንደሚሰጥ አስታውቋል። የፕሬዚዳንት ኦባማ አስተዳደር የአልሸባብ መሪዎችን ለሚጠቁሙ 33 ሚሊዮን ዶላር መመደቡን ማስታወቁ ይታወሳል።

ሼክ ሸንጎሌ  ተደጋጋሚ የግድያ ሙከራዎችን ማምለጣቸውን ፕሬዚዳንት ቡሽን እንደተዋጉት ሁሉ ኦባማንም እንደሚዋጉ ገልጠው፣ አሜሪካ መንግስት አቀረብኩ ለሚለው አዲሰ እቅድም አሜሪካዊያንን በመጥለፍ እንደሚበቀል ዝቷል።

አልሸባብ ከአልቃይዳ ጋር በይፋ መቃላቀሉን ካስታወቀበት ጊዜ ጀምሮ እየተዳከመ መምጣቱ ይነገራል። ምንም እንኳ ታጣቂ ሀይሉ አሁንም ሰፊ የሶማሊያን ግዛት ተቆጣጥሮ የያዘ ቢሆን፣ ከአፍሪካ ህብረት ጦር እየደረሰበት ባለው ጥቃት፣ ቀሪ ይዞታዎችን ሊያጣ ይችላል የሚሉ ግምቶች እየተሰነዘሩ ነው።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming