ታጋይ ፍሰሃ አብርሃ አረፈ

የካቲት 21 ቀን 2004 ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-የቀድሞ መከላከያ ሚንስትር ና የህወሓት መስራች የሆኑት የአቶ ስዬ አብርሃ የሶስት ጊዜ ታናሽ ወንድም የሆነው ታጋይ ፍሰሃ አብረሃ ዛሬ ሌሊት ህይወቱ አለፈ፡፡

ፍሰሃ ከ1971 ዓ.ም ጀምሮ የህወሃት ታጋይ የነበረ ሲሆን፤ ከመንግስት ለውጥ በኋላ በተንቤን አውራጃ የሀገረ ሰላም አስተዳዳሪ ሆኖ ሰርቷል።

በ1993ዓ.ም የተከሰተውን የህወሓት ክፍፍል ተከትሎ አቶ ስዬ አብርሃ ሲታሰሩ ፣ ፍሰሃም ለአራት አመት ያህል አብሮአቸው ታስሮአል፡፡

የአራት ልጆች አባት የሆነው ፍሰሃ አብረሃ ከጥቂት ሰአት በኋላ አስክሬኑ ወደ ትውልድ መንድሩ ተንቤን እንደሚላክ ተመስገን ደሳለኝ በፌስ ቡክ ላይ የለጠፈው ዜና ያመለክታል።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide