በከምሴ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ድዋ እንዳያደርጉ ተከለከሉ

ግንቦት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በከምሴ ልዩ  ዞን ውስጥ ነዋሪ የሆኑ ሙስሊሞች ባለፈው አርብ ሶላት ሊያደርጉ በከተማዋ መሀል አደባባይ በሚገኘው መስጊድ ውስጥ  ለመሰባሰብ ጉዞ ሲጀምሩ በርካታ የፌደራል ፖሊስ አባላት አካባቢውን ተቆጣጥረዋል። ነዋሪዎቹ ከመስጊዱ ግቢ አልፈው  በአስፓልቱ ላይ በመቆማቸው የከተማው ትራፊኮች  ከአዲስ አበባ ወደ ደሴ እና ከደሴ ወደ አዲስ አበባ የሚሄዱትን መኪኖች  ጉዞአቸው እንዲያቆሙ ለማድረግ ተገደዋል።

በፌደራል ከባድ መሳሪያዎች የተከበቡት ሙስሊሞች ሶላታቸውን  እንደጨረሱ፣ ፌደራል ፖሊሶች ወደ መስጊዱ ገብተው አባረዋቸዋል። አንድ ስማቸው እንዳይጠየቅ የፈለጉ በእድሜ የገፉ አዛውንት፣ እንደተናገሩት ሙስሊሞች ከሶላት ውጭ ድዋ ወይም ስብሰባ ማካሄድ እንደማይችሉ ተነግሯቸዋል። ሙስሊሞቹ ወደ ሌላ አካባቢ በመሄድ ሲሰባሰቡ ፣ የፌደራል ፖሊሶች ወደ ቦታው በመሄድ በድጋሜ እንዲበተኑ አድርገዋል።

ምንጮች እንደገለጡት በነገው ሶላት ምናልባትም ግጭት ሊነሳ ይችላል የሚልፍ ከፍተኛ ፍርሀት አለ።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide