በአዲስ አበባ የሕዝብ ት/ቤቶች በመንግስት ተወረሱ

ግንቦት ፳፫ (ሃያ ሦስት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ ውስጥ ከሚገኙት 117 የህዝብ ትምህርት ቤቶች መካከል 115 ያህሉ ወደ መንግስት ትምህርት ቤትነት በያዝነው ዓመት ተዘዋወሩ፡፡

በህዝብ ይተዳደሩ የነበሩ ትምህርት ቤቶች ወደ መንግስት የተዛወሩት በህብረተሰቡ ጥያቄ መሰረት መሆኑን የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ይግለጽ እንጂ ሕዝቡ የት እና መቼ  ጥያቄ እንዳቀረበ ያብራራው ነገር የለም፡፡

በህዝብ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሲያስተምሩ የነበሩ መምህራንና ሰራተኞች ምድባ በአዲስ መልክ እየተዘጋጀ መሆኑንም ቢሮው በትላንትናው ዕለትበሰጠው መግለጫ አስታውቋል ;; በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው አንድ የአዲስ አበባ መምህራን ማህበር አመራር አባል በሰጡት አስተያየት የሕዝብ ት/ቤቶቹ ከፍለው ለመማር ለሚችሉ ጥሩ አማራጭ ነበሩ፡፡እውነት ለመናገር ከመንግስት ት/ቤቶች የተሻለ ብቃት ያላቸውም ናቸው፡፡ መንግስት በወሰደው እርምጃ የትምህርት ጥራቱ ወደ ኃላ እንዳይመለስ ሥጋት አለኝ ብለዋል፡፡

በፈለገዮርዳኖስ ት/ቤት ተማሪ የነበረ አንድ አስተያየት ሰጪም ውሳኔው አሳዛኝ ነው ብሎታል፡፡ “ እኛ ተማሪ በነበርን ግዜ በተመጣጣኝ ክፍያ ከፍተኛ ትምህርት እናገኝ ነበር፡፡በዚህ ላይ የመንግስት ት/ቤቶች ግማሸ ቀን ሲያሰተምሩ እኛ ግን ሙሉ ቀን እንማር ነበር፡፡በየሳምንቱ ትምህርታዊ ውድድሮች ሁሉ ስለነበሩ እርስ በርስ የነበረን ፉክክር ከፍተኛ ነበር፡፡ይህ ሁሉ በመንግስት ት/ቤቶች እንዴት ማግኘት ይቻላል” ሲል ጠይቋል፡፡

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide