በሰሜን ጎንደር የሚገኘው የመኢአድ ጽህፈት ቤት አባሎቻቸው በገፍ መታሰራቸውን ገለጠ

ሰኔ ፬ (አራት) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:-ጽህፈት ቤቱ ለኢሳት በላከው መረጃ እንዳመለከተው በኢትዮጵያ ውስጥ በዜጎች ላይ የሚደርሰው እስራት፣ ግርፋት፣ ስደትና ረሀብ ከልክ አልፎአል ብሎአል።

በሰሜን ጎንደር በጭልጋ ወረዳ የመኢአድ ም/በት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ መለሰ አስሬ ግንቦት23 ከቀኑ በ10 ሰአት ከ10 በላይ በታጠቁ የፌደራል ፖሊሶች በሀይል ተወስደው የደረሱበት አለመታወቁን፣ የጃናሞራ ወረዳ መኢአድ ም/ቤት ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ስለሺ ጥጋቤነህ ግንቦት 23 ከቀኑ በ10 ሰአት ደባርቅ ከሚገኘው መኖሪያ ቤቱ በፌደራል ፖሊሶች በሀይል መወሰዱና የደረሰበት አለመታወቁን ገልጧል።

በማግስቱ ደግሞ የሰሜን ጎንደር መኢአድ ጽህፈት ቤት የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ የሆኑት አቶ ታድሎ ተፈራ በፌደራል ፖሊሶች ተወሰደው የደረሱበት አለማታወቁን እንዲሁም አቶ ካሳሁን በክረጽዮን ከሚኖሩበት የወቅን ከተማ ተወስደው መደብደባቸውን፣ መታሰራቸውን፣ ቤታቸው መዘረፉንና ሀብት ንብረታቸውን መቀማታቸውን ድርጅቱ ገልጧል።

ኢሳት የሰዎችን ታፍኖ መወሰድ በተመለከተ ባለፈው ሳምንት ዘገባ ማቅረቡ ይታወሳል። ታፍነው የተወዱት ሰዎች በህይወት ይኑሩ አይኑሩ የታወቀ ነገር የለም።

___________________________________________________________________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide