በመልጋ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ በወንዶገነትም ተመሳሳይ ተቃውሞ ተነስቷል።

ሐምሌ ፲፱ (አስራ ዘጠኝ) ቀን ፳፻፬ ዓ/ም

ኢሳት ዜና:- ከሶስት ቀናት በፊት በሲዳማ ዞን በመልጋ ወረዳ የተነሳው ተቃውሞ ወደ ወንዶገነትም ተዛምቶ፣ የባሻ ወረዳ ሊቀመንበር መገደሉንና የወረዳው መስተዳደር መኪና መቃጠሉን ዘጋቢያችን ገልጧል። በግጭቱም ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ፣ ነገር ግን በርካታ ቁጥር ያላቸው ፖሊሶች መቁሰላቸው ታውቋል።

ሁለቱ ወረዳዎች ኩታገጠም ሲሆኑ፣ በመልጋ የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የወረዳው ባለስልጣናት ህዝቡን ለማሳመን ወደ ታች ወርደው በሚነጋገሩበት ጊዜ ነው ግጭቱ የተነሳው።

በእነዚህ አካባቢዎች ያለው አብዛኛው ሰው በከብት ርቢ የሚተዳደር የነፍስ ወከፍ መሳሪያ የታጠቀ መሆኑ ፣ በወረዳ ባለስልጣናት እና በፖሊሶች ላይ የሚደርሰውን ጉዳት እንዳባባሰው ዘጋቢያችን አክሎ ገልጧል።

መልጋ እና ወንዶገነት ወረዳዎች አሁንም በፌደራል ልዩ ሀይል ቁጥጥር ሲሆኑ፣ ዜናውን እስካጠናከርንበት ሰአት ድረስ ውጥረት እናደለ ዘጋቢያችን ገልጧል።

በመልጋ ወረዳ ወረዳ ሰሞኑን በተነሳው ግጭት 12 የፌደራል ፖሊስ አባላትና ከ20 በላይ ሲቪሎች መቁሰላቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

የዞኑ ነዋሪዎች ክልል የመሆን ጥያቄያችን መልስ እስካላገኘ ድረስ ግብር አንገብርም በማለት ጠንካራ አቋም ይዘዋል።

የክልሉ ምክርቤት ከትናንት በስቲያ ስብሰባ ቢያካሂድም በዞኑ ስላለው ግጭት ምንም ውሳኔ ሳያሳልፍ ተበትኖአል።

_____________________________________________________________________________________________

ESAT is the first independent Ethiopian satellite service tasked to produce accurate and balanced news and information, as well as other entertainment, sports and cultural programming created for and by Ethiopians.

ESAT is committed to the highest standards of broadcast journalism and programming and will strive to provide an outlet of expression to all segments of the diverse Ethiopian community worldwide